Загрузка...

የአባትነት መብቱ ተከበር#ethiopia #ebs #history Ethiopia #duet #ኢትዮጵያ Ethiopia #habesha #ታሪክ

ፍርድ ቤቱ የአባትነት መብቱ እንዲከበር ወስኗል!!🥹🤔

የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዋንትያ ሰለሞን እና በልጇ አባት መካከል ለወራት ሲያከራክር በቆየው የሕፃን ልጅ የመጎብኘት መብት ጉዳይ ላይ ውሳኔ አሳለፈ።

የልጅቷ አባት የሆኑት አመልካች፣ "ልጄን እንዳልንከባከባትና እንዳልጎበኛት ተከልክያለሁ" በሚል ለፍርድ ቤት ባቀረቡት አቤቱታ፣ የመጎብኘትና የመንከባከብ መብታቸው እንዲከበር ጠይቀው ነበር።

ተጠሪ ዋንትያ ሰለሞን ለቀረበባት ክስ በሰጠችው ምላሽ፣ አመልካች ከዚህ ቀደም አባትነቱን ክዶ ሲከራከር እንደነበርና በወቅቱ በገንዘብ እጥረት ምክንያት የዲ ኤን ኤ ምርመራ ባለመደረጉ መዝገቡ ተዘግቶ እንደነበር አስታውሳለች።

አክላም፦አመልካች አባትነቱ በሕግ ሳይረጋገጥ ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት የለውም፤ ልጇን በአግባቡ እየተንከባከበች እንደሆነና ህፃኗን የሚጎዳ ምንም ዓይነት ተግባር (ቪዲዮ) እንዳልሰራች፤ አባትነቱን ክዶ የቆየና ቀለብ ቆርጦ የማያውቅ ሰው ሕፃኗን እንዲጎበኝ መፍቀድ ለልጅቷ ደህንነት ተገቢ አይደለም፤ የሚሉ ነጥቦችን በማንሳት ክሱ ውድቅ እንዲደረግላት ተሟግታለች።

ጉዳዩን ሲመረምር የቆየው የንፋስ ስልክ ላፍቶ ምድብ 4ኛ ቤተሰብ ችሎት፣ የግራ ቀኙን ክርክር ከመረመረ በኋላ የሚከተለውን ውሳኔ አስተላልፏል፦
1. የአባትነት መብት
አመልካች የልጅቷ አባት ከመሆናቸው አኳያና የሕፃናት መብት ወላጆቻቸውን የማወቅና የመንከባከብ መብትን የሚደግፍ በመሆኑ አባትየው የመጎብኘት መብት አላቸው።
2. የማስረጃ እጥረት
ተጠሪ (ዋንትያ) አመልካች ልጃቸውን እንዳይጎበኙ የሚያደርግ በቂ የሰነድም ሆነ የሰው ምስክር ማስረጃ አላቀረበችም።
3. የጉብኝት መርሃ-ግብር
አመልካች ዘወትር እሁድ በሳምንት አንድ ጊዜ ልጃቸው በሚኖሩበት የተጠሪ ቤት በመሄድ፣ ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 11:00 ሰዓት ድረስ የመጎብኘትና የመንከባከብ መብት እንዲኖራቸው ፍርድ ቤቱ ወስኗል።

ይህ ውሳኔ በሕፃናት መብት ኮንቬንሽን እና በሀገሪቱ የቤተሰብ ሕግ ላይ የተደነገጉ የወላጅና የልጅ ግንኙነት መብቶችን መሠረት ያደረገ መሆኑ ተመልክቷል።
መረጃው የዘ- ሐበሻ ነው ።
#ethiopia #ebs #history Ethiopia #duet #ኢትዮጵያ Ethiopia #habesha #ታሪክ

Видео የአባትነት መብቱ ተከበር#ethiopia #ebs #history Ethiopia #duet #ኢትዮጵያ Ethiopia #habesha #ታሪክ канала Phanos Ethiopia
Яндекс.Метрика
Все заметки Новая заметка Страницу в заметки
Страницу в закладки Мои закладки
На информационно-развлекательном портале SALDA.WS применяются cookie-файлы. Нажимая кнопку Принять, вы подтверждаете свое согласие на их использование.
О CookiesНапомнить позжеПринять