Загрузка...

በአፍሪካዊው ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ ባለቤትነት የሚመራው ግዙፉ የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ // ሳሪስ ቲቪ

አሊኮ ዳንጎቴ አፍሪካንውያን ሆይ አትጨነቁ እያሉ ነው

#Ethiopia | በአፍሪካዊው ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ ባለቤትነት የሚመራው ግዙፉ የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ለተለያዩ የአፍሪካ አገራት የነዳጅ ኤክስፖርት መጀመሩን አስታወቀ። ፋብሪካው 456 ቶን ነዳጅ ለሽያጭ ያቀረበ ሲሆን፣ የመጀመሪያዎቹ ገዢዎችም አይቮሪ ኮስት፣ ካሜሮን፣ ታንዛንያ እና ቶጎ መሆናቸው ተገልጿል።

በናይጄሪያ የሚገኘው ይህ ማጣሪያ በቀን 650 ሺህ በርሜል ነዳጅ የማጣራት አቅም ያለው ሲሆን፣ የናይጄሪያን ፍላጎት አሟልቶ ለውጭ ገበያ የሚተርፍ ምርት እያመረተ ይገኛል።

በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ግጭት ምክንያት የተከሰተውን የኃይል አቅርቦት እጥረት እና የዋጋ ንረት ለመቋቋም ኤክስፖርቱ በአፋጣኝ እንዲጀመር ተደርጓል።

ይህ ጅምር ለምስራቅ፣ ምዕራብ እና መካከለኛው አፍሪካ አገራት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለመፍጠር ትልቅ ተስፋ ሆኗል።

ፋብሪካው በ2024 ሥራ ከመጀመሩ በፊት ናይጄሪያ የነዳጅ ፍላጎቷን ሙሉ በሙሉ ከውጭ በማስገባት ታሟላ ነበር፤ አሁን ግን ላኪ መሆን ችላለች።

የፋብሪካው ቃል አቀባይ እንደገለጹት ከአፍሪካ አገራት በተጨማሪ ከሌሎች አህጉራትም ከፍተኛ የነዳጅ ፍላጎት እየቀረበላቸው ይገኛል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

#getutemesgen #getu #ጌጡ
#DangoteRefinery #AlikoDangote #NigeriaEconomy #AfricaEnergy #FuelExport #OilAndGas #EconomicIntegration #africanewsupdate
#SarisTV #ሳሪስ_ቲቪ

Видео በአፍሪካዊው ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ ባለቤትነት የሚመራው ግዙፉ የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ // ሳሪስ ቲቪ канала SARIS TV | ሳሪስ ቲቪ
Яндекс.Метрика
Все заметки Новая заметка Страницу в заметки
Страницу в закладки Мои закладки
На информационно-развлекательном портале SALDA.WS применяются cookie-файлы. Нажимая кнопку Принять, вы подтверждаете свое согласие на их использование.
О CookiesНапомнить позжеПринять